PAUL VS JAMES
ይህ ጥያቄ በክርስቲያን ማህበረሰብ መካከል፣ ብዙ ጊዜ፣ ሲነሳ ይስተዋላል፣ ጥያቄው፣የቆየ ጥያቄ ነው። ማለትም ጳውሎስ እና ያዕቆብ በእምነት እና በስራ ላይ የተለያዩ አመለካከቶችን ያቀርባሉ፣ የሚለው ክስ ብዙውን ጊዜ ይነሳል።
እንደውም፣ አንዳዶች፣ መፀሐፍ ቅዱስ፣ እርስ በርሱ ይጋጫል፣ ይላሉ፣ የጳውሎስን ለመቀበል፣ ብዬ፣ የያቆብን ልቅደደው ፣ልሰርዘው ወይ እስኪሉ ድረስ፣ ጉንጭ አልፋ ንግግር ሲደርጉ ይታያል። እስኪ እኔ ና እናንተ የሁለቱንም ሀሳብ፣ ከወገንተኝነት በነፃ፣ በአጉል፣ ሐይማኖተኝነትም፣ ቀንበር ሳንጠመድ፣ ክፍሉ፣ ምን እያለ ነው? እውነት ይሔንን ያህል፣ ሀሳቡ፣ ከባድ ነው ወይ? እርስ በእርሱስ ይጣረሳል ወይ? የሚለውን አብረን፣ ዳበስ፣ፈተሽ እናድርገው።
📖💥 ሐዋርያው፣ጳውሎስ ምን አለ?
ጳውሎስ በሮሜ 3፥28 እንዲህ ይላል
📌“ሰው ያለ ሕግ ሥራ በእምነት እንዲጸድቅ እንቆጥራለንና።”
— ሮሜ 3፥28
📌ኤፌሶን 2፥8 -9
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁸ ጸጋው በእምነት አድኖአችኋልና፤ ይህም የእግዚአብሔር ስጦታ ነው እንጂ ከእናንተ አይደለም፤
⁹ ማንም እንዳይመካ ከሥራ አይደለም።
💢 ተወዳጁ፣ #ጳውሎስ #በእምነት #መዳን #እንጂ #በስራ #አለመሆኑን #ያስተምራል። 👉ይህም ማለት #ሰው #በእምነት #ብቻ #እንደሚድን #እንጂ #በስራው #መልካምነት #ወይም #በሃይማኖታዊ #ተግባራት #እንዳልሆነ #ያመለክታል።
👉ጳውሎስ ይህንን በማስረዳት በሕገ-ልማድ ስራዎች ሳይሆን በእምነት መዳንን እረገጥ እና ጠቅጠቅ አድርጎ ያስተምራል፣ (ሮሜ 3፥28) ማስታወስ፣ ግድ ይላል።
💢💥ያዕቆብ (ያዕቆብ 2፥14-26)
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
👉ያዕቆብ ምን አለ?
።።።።።።።።።።።።።።።
ያዕቆብ 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁴ ወንድሞቼ ሆይ፥ እምነት አለኝ የሚል፥ ሥራ ግን የሌለው ሰው ቢኖር ምን ይጠቅ መዋል? እምነቱስ ሊያድነው ይችላልን?
¹⁵ ወንድም ወይም እኅት ራቁታቸውን ቢሆኑ የዕለት ምግብንም ቢያጡ፥
¹⁶ ከእናንተ አንዱም፦ በደኅና ሂዱ፥ እሳት ሙቁ፥ ጥገቡም ቢላቸው ለሰውነት ግን የሚያስፈልጉትን ባትሰጡአቸው ምን ይጠቅማቸዋል?
¹⁷ እንደዚሁም ሥራ የሌለው እምነት ቢኖር በራሱ የሞተ ነው።
¹⁸ ነገር ግን አንድ ሰው፦ አንተ እምነት አለህ እኔም ሥራ አለኝ፤ እምነትህን ከሥራህ ለይተህ አሳየኝ፥ እኔም እምነቴን በሥራዬ አሳይሃለሁ ይላል።
¹⁹ እግዚአብሔር አንድ እንደ ሆነ አንተ ታምናለህ፤ መልካም ታደርጋለህ፤ አጋንንት ደግሞ ያምናሉ ይንቀጠቀጡማል።
²⁰ አንተ ከንቱ ሰው፥ እምነት ከሥራ ተለይቶ የሞተ መሆኑን ልታውቅ ትወዳለህን?
²¹ አባታችን አብርሃም ልጁን ይስሐቅን በመሠዊያው ባቀረበ ጊዜ በሥራ የጸደቀ አልነበረምን?
²² እምነት ከሥራው ጋር አብሮ ያደርግ እንደ ነበረ፥ በሥራም እምነት እንደ ተፈጸመ ትመለከታለህን?
²³ መጽሐፍም፦ አብርሃምም እግዚአብሔርን አመነ ጽድቅም ሆኖ ተቈጠረለት ያለው ተፈጸመ፤ የእግዚአብሔርም ወዳጅ ተባለ።
²⁴ ሰው በእምነት ብቻ ሳይሆን በሥራ እንዲጸድቅ ታያላችሁ።
²⁵ እንደዚሁም ጋለሞታይቱ ረዓብ ደግሞ መልእክተኞቹን ተቀብላ በሌላ መንገድ በሰደደቻቸው ጊዜ በሥራ አልጸደቀችምን?
²⁶ ከነፍስ የተለየ ሥጋ የሞተ እንደ ሆነ እንዲሁ ደግሞ ከሥራ የተለየ እምነት የሞተ ነው።
🎯💥 ያቆብ፣ በመልዕክቱ፣ መዳን፣ በስራ ነው አላለም፣ በእምነት የሚገለጥ ስራ እንዳለበት አስተማረ፣እንጂ።
👉ያዕቆብ ያለው #እምነት #ያለ #ስራ #ሙት #እንደሆነ #ነው ስለዚህ፣ ያዕቆብ #እምነት #በስራ #መገለጥ #እንዳለበት እረገጥ ና ጠቅጠቅ አድርጎ አስተማረ።
📌ማጠቃለያችን፦
።።።።።።።።።።።።።
👉#ጳውሎስ እና #ያዕቆብ #እርስ #በርስ #አይጋጭም።
👉#ጳውሎስ #በእምነት #መዳንን #ሲያስተምር፣
👉#ያዕቆብ #ደግሞ #እምነት #በስራ #መገለጥ #እንዳለበት #ያሳያል።
👉 ጳውሎስ #በእምነት #መዳን #እንጂ #በስራ #አለመሆኑን #ሲያስተምር
👉ያዕቆብ #ደግሞ #እውነተኛ #እምነት #በስራ #የሚገለጥ ና የሚታይ #እጅ ያለው፣ የሚዘረጋ #እግር ያለው፣ የሚንቀሳቀስ፣ ወደላይ ብቻ ሳይሆን፣ ወደጎን #የሚያድግ #የሚያድግ #መሆኑን #አስተማረ እንጂ፣ የተለ ወንጌል፣ አልፈፀመም፣ ከጳውሎስም ሀሳብ ጋር አልተጋጨም።
💢በሌላ አነጋገር #ጳውሎስ #መዳንን #ሲያብራራ #ያዕቆብ #ደግሞ #የእምነትን #መገለጫ፣ ማሳያ መንገዱን አብራራልን።
💢 ሁለቱም አስተምህሮቶች #እምነት እና #ስራ #አብረው #መሄድ #እንዳለባቸው #ያሳያሉ፣ እንጂ በጭራሽ፣ አይጋጩም። 🙏
።።።።።።።።።።።።።።።።።
©DANIEL W.











































































